
ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/መሰ/የኅብረት ስራ ማህበር
”በጋራ እንችላለን ”
- shegersmartsc@gmail.com
- +251945051115/+251118550035
”በጋራ እንችላለን ”
ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማህበር የ7ተኛውን መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አከናወነ፡፡
ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማህበር የ7ተኛውን መደበኛ የጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተግባረዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተሳካ ሁኔታ አከናውኗል፡፡
ጠቅላላ ጉባዔውን የማህበራችን ሰብሳቢ በሆኑት አቶ ቁምነገር ማስረሻ አቅራቢነት እና የአዲስ አበባ የህብረት ስራ ኮሚሽን የተወከሉ አካላት በተገኙበት አጀንዳዎችን በማጸደቅ ተከፍቷል፡፡
በዕለቱ በቀረቡት አጀንዳዎች፦
1.የህብረት ስራ ማህበሩን የ2017 በጀት ዓመት የ7 ወር የተከናዎኑ ተግባራትን ሪፖርት ማዳመጥና ተወያይቶ ማፅደቅ፣
3 .የህብረት ስራ ማህበሩን የ2016 በጀት ዓመት ሂሳብ የውጭ ኦዲት ሪፖርት ማዳመጥና ተወያይቶ ማፅደቅ፣
የህብረት ስራ ማህበሩን የ2017 በጀት ዓመት የ7 ወር የተከናዎኑ ተግባራትን ሪፖርት በማህበሩ ሰብሳቢ አቶ ቁምነገር ማስረሻ የቀረበ ሲሆን የቁጥጥር ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ በላይነው አሻግሬ የህብረት ስራ ማህበሩን የ2017 በጀት ዓመት የ7 ወር የቁጥጥር ኮሚቴ ሪፖርት አቅርበው ሰፊ ውይይት እና ጥያቄዎች ከተሳታፊው የቀረበ ሲሆን ለቀረቡ ጥያቄዎች የማህበሩ ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት መኮንን ምላሽ ሰጥተውበታል፡፡
በመቀጠልም የኅብረት ሥራ ማህበሩን የ2016 በጀት ዓመት የሂሳብ ኦዲት ከአዲስ አበባ የገ/ቁ/ብ/ህ/ስ/ማህበራት ፌደሬሽን በመጡ ኦዲተሮች ኦዲት ተደርጎ የኦዲት ሪፖርቱ ለጠቅላላ ጉባኤ ቀርቦ ከአባላት ለቀረበ ጥያቄዎች በአቅራቢ ኦዲተሯ ምላሽ ተሰጥቶበት በሙሉ ድምጽ የኦዲት ሪፖርቱ ጸድቋል፡፡
የኅብረት ሥራ ማህበሩ ለመጪው ግዜ የ200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ተጨማሪ ሼር/ዕጣ ለጠቅላላ ጉባዔው በማቅረብ አጸድቆ ማሳወጅ ተችሏል፡፡
የማህበሩን የተጓደሉ እና ተጠባባቂ የሽምግልናና ግልግል ኮሚቴ አባላትን ለማስመረጥ ከተጠቆሙ ሶስት አባላት አብላጫ ድምጽ በማግኘት አቶ ምስጋናው በዛብህ ተመርጠዋል፡፡
በዕለቱም ከአዲስ አበባ ኅብረት ሥራ ማኅበራት ማደራጃ የተወከሉ አካላት የተገኙ ሲሆን በውይይቱም አባላት ለሸገር ኅብረት ሥራ ማኅበር ማደግ የሚበጁ ጠቃሚ ምክረ ሀሳቦችን ሰጥተዋል። በመጨረሻም ከአዲስ አበባ ህብረት ስራ ኮሚሽን ተወካይ በአቶ ብዟየሁ አማካኝነት የመዝጊያ ንግግር በማድረግ የሸገር ገ/ቁ/ብ/ሃላ/የተ/መ/ህ/ስ/ማህበር የ7ኛ መደባኛ ጉባኤ በስኬት ተጠናቋል።
ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር የተመሰረተበትን 4ተኛ ዓመት ባከበረበት መጋቢት 16 2017 ዓ.ም በሰራተኞች እና በአባላት የሚተገበር “ፕሮጀክት 120” የተሰኘ ለአባላት ልዩ ጥቅም የሚያስገኝ ንቅናቄ የስራ አመራር ሰብሳቢ አቶ ቁምነገር ማስረሻ እንዲሁም የማህበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ትግስት መኮንን፣ ከማኔጅመንት አባላት፣ የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች እና የማህበሩ ጠቅላላ ሰራተኞች በተገኙበት ይፋ /launch/ ተድርጓል::
ስለ ፕሮጀክቱ አካሄድ እና አፈጻጸም አጭር ገለጻ በአቶ ሀይለማርያም ወንድምነህ የቀረበ ሲሆን በቀጣይ በዘመቻ መልክ ለቅርንጫፍ ቢሮዎች በተሰጣቸው አቅጣጫ የሼር ሺያጭ ከተሰጣቸው ኮታ በላይ አፈፃፀም ያስመዘገቡ የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች በማህበሩ የምስጋና እና የዕዉቅና ሰርተፍኬት ተስጥቷቸዋል ::
ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር የማህበሩን የ4ተኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ከጠቅላላ ሰራተኞቹ ፤ ከስራ አመራር ኮሚቴ እና ከተለያዩ ኮሚቴዎች ጋር ሰንጋተራ በሚገኘው ዋና ቢሮ በመጋቢት 16 ቀን 2017 ዓ.ም በደመቀ መልኩ አክብሯል፡፡ የምስረታ በዓሉን የከፈቱት የሥራ አመራር ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ቁምነገር ማስረሻ የማህበሩን አመሰራረት ታሪካዊ ዳራ እና አሁናዊ የማህበሩን ቁመና በማስገንዘብ ሰራተኛው እና አመራሩ የበለጠ መትጋት እና የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚጠበቅበት አስገንዝበዋል፡፡ በተጨማሪም አሁን ባለንበት ወቅት የፋይናንስ ዘርፉ ገና ምንም ያልተሰራበት እና ብዙ መስራት የሚጠይቅ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ በመጨረሻም ለታዳሚዎቹ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት በማስተላለፍ የበዓሉን መከፈት አብስረዋል፡፡ በማስከተልም በቢዝነስ ልማት እና ቅርንጫፍ ማስተባበር ስራ አስኪያጅ በሆኑት በአቶ ምስጋናው አየለ ጋባዥነት በማህበሩ ስራ አመራር ሰብሳቢ እና በማናጅመት አባላት ለ4ተኛ ዓመት የምስረታ በዓል የተዘጋጀውን የሻማ ማብራት ስነ ስርአት እና የኬክ ቆረሳ በጋራ አከናውነዋል፡፡ በመጨረሻ በስራ አመራር ሰብሳቢ እና በዋና ስራ አስኪያጅ በተሰጠ የቀሪ ግዜ የስራ አቅጣጫ እና የቃል መግባት ስነስርዓት በማከናወን የበዓሉ አከባበር ተጠናቋል፡፡
ጥር 28/05/2017 “የህብረት ሥራ ማህበራት ሚና ለኢትዮጵያ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳር ህብረት ሥራ ኮሚሽን በጋራ ያዘጋጁት የኅብረት ሥራ ማኅበራት ኤግዚቢሽን ባዘርና ሲምፖዚየም ተከፍቷል፡፡ የኤግዚቢሽን፤ ባዛርና ሲምፖዚየሙ ከጥር 28 እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም ለ5 ተከታታይ ቀናት የሚካሄድ ሲሆን ማህበራችን ሸገር የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኃ/የተ/መሰ/ኀ/ስ/ማ በዚሁ ኤግዚቢሽን ባዘርና ሲምፖዚየም ላይ በመሳተፍ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በእግዚቢሽንና ባዛሩ ለሚሳተፉ የህብረተሰብ ክፍሎች በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል፡፡
የሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር መሰረታዊ የህብረት ስራ ማህበር የማኔጅመንት አባላት፣ከፍተኛ ባለሙያዎችና የቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆች በአሚጎስ የገንዘብ ቁጠባ ብድር መሰረታዊ የህብረት ስራ ማህበር ቢሮ በመገኘት የልምድ ልውውጥ አድርገዋል፡፡ የልምድ ልውውጡ ዋና ትኩረት የተቋሙን የሰው ሀይል አደረጃጀት፣ የፋይናንስ አሰራር፣ ድጅታል አሰራር፣ የስጋት ትንበያ አስተዳደር፣ የአባላት አያያዝና እርካታ እና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዙሪያ ሲሆን የተቋሙ ትምህርትና ስልጠን ክፍል ሃላፊ የሆኑት አቶ ሀጎስ እና የፕላንና በጀት ክፍል ሃላፊ የሆኑት አቶ ሳምሶን በተገኙበት አጠቃላይ ስለተቋማቸው አሰራርና ከላይ በተጠቀሱት ርእሰ ጉዳዮች ላይ ጥልቅ የሆነ ገለጻ የተደረገ ሲሆን በቀጣይ በየስራ ክፍል ራሱን ችሎ ልምድ ልውውጥ እንደሚኖር በመግባባት እና የአሚጎስን የቢሮ አደረጃጀት በመጎብኘት የእለቱን ልምድ ልውውጥ አጠናቀናል ፡፡
በጋራ እንችላለን!!!!!!!!
ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር እና አሐዱ ባንክ አክሲዮን ማኅበር በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ፡፡
የስምምነቱ መሰረታዊ ዓላማ የፋይናንስ ተደራሽነትን የተሻለ ለማድረግ፣ የፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ትብብር ለመፍጠርና በአጠቃላይ ቁጠባን በማበረታታት ሀብት ለማሰባሰብና የብድር ፍላጎትን ለማሟላት ታሳቢ ያደረገ ነው::እንደሚታወቀው አሐዱ ባንክ ከብድር የእቅድ በጀቱ ላይ 15℅ የሚሆነውን ለታችኛው የኅብረተሰብ ክፍል ለማበደር ቁርጠኝነቱ አለው:: በመሆኑም ይህ ስምምነት ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ በተመረጡት የትብብር ማዕቀፎች ላይ በጋራ የሚሰራ ይሆናል::
ነሐሴ 30/ 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ~ ኢትዮጵያ
ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/መሰ/ኅብረት ሥራ ማኅበር ነሐሴ 21 ቀን 2014 ዓ.ም በአባላት ተወካዮች አማካኝነት 3ተኛ መደበኛ ጉባኤውን በካፒታል ሆቴል በተሳካ ሁኔታ አጠናቋል::
በእለቱ በቀረቡ አጀንዳዎች ማለትም:-
1. የ2014 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ማዳማጥና ውሳኔ ማሳለፍ
2. የቁጥጥር ኮሚቴ ሪፖርት ማዳመጥና ውሳኔ ማሳለፍ
3. የ5 ዓመት ስትራቴጅክ እቅድ ዝግጅት ማዳመጥና ውሳኔ ማሳለፍ
4. የ2015 በጀት ዓመት እቅድ ዝግጅት ማዳመጥና ውሳኔ ማሳለፍ
5. በመተዳደሪያ ደንብና በብድር መመሪያው ላይ የማሻሻያ አንቀጾችን አዳምጦ ውሳኔ ማሳለፍ በሚሉት አጀንዳዎች ላይ ጉባኤተኛው ተወያይቶ ጠቃሚ ውሳኔዎችን አሳልፏል:: ከአዲስ አበባ ኅብረት ሥራ ማኅበራት ማደራጃ የተወኩሉ አካላት በእለቱ ተገኝተው ለሸገር ጠቃሚ የሚሆኑ ሃሳቦችን ሰጥተዋል:: ሸገር እስከዚህ ወር ድረስ 47 ሚሊዮን ብር ካፒታልና 1832 አባላት አለው:: ይህ አፈፃፀም የአንድ ዓመት ከአምስት ወር ሥራ ውጤት ነው::
በጋራ እንችላለን!!!
ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/መሰ/ኅብረት ሥራ ማኅበር 6ተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ !!
ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/መሰ/ኅብረት ሥራ ማኅበር በቀን 27/11/2016 ዓ.ም አባላት እና ተወካዮች በተገኙበት 6ተኛ መደበኛ ጉባኤውን በኢትዮጵያ ሆቴል በተሳካ ሁኔታ አጠናቋል::
በእለቱ በቀረቡት ፦
1.የህብረት ስራ ማህበሩን የ2016 በጀት ዓመት የተከናዎኑ ተግባራትን ሪፖርት ማዳመጥና ተወያይቶ ማፅደቅ።
2. የህብረት ስራ ማህበሩን የ2016 በጀት ዓመት የቁጥጥር ኮሚቴ ሪፖርት ማዳመጥ፦
3 .የህብረት ስራ ማህበሩን የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ማዳመጥና ተወያይቶ ማፅደቅ
4. የተለያዩ የብድር መመሪያ ማሻሻያዎች ማቅረብና ተወያይቶ ማፅደቅ
5. በህብረት ስራ ማህበሩ አባላት በማፍራት፣ብድር ወስዶ በወቅቱ በመመለስ እና ሳያቆራርጡ ለቆጠቡ አባላት የምስጋና ወረቀት መስጠት በሚሉት አጀንዳዎች ላይ ጉባኤተኛው በሰፊው ተወያይቶ ጠቃሚ ውሳኔዎችን አሳልፏል::
ከእነዚህ መካከል ያለውን የገንዘብ የመግዛት አቅምና የገበያ ሁኔታ ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት
Ø ለንግድ ጉዳይ እስከ1,000,000.00 የነበረው ወደ 1,200,000 ከፍ እንዲል
Ø ለመኪና እስከ 2,000,000.00 የነበረው ወደ 2,500,000.00 ከፍ እንዲል
Ø ለቤት 3,000,000.00 የነበረው ወደ 4,000,000.00 ከፍ እንዲል በጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ተላልፏል::
Ø ከዚህ በተጨማሪ የአጭር ጊዜ የብድር አማራጮች ምክረ ሃሳብ በአመራሩ ቀርቦ በጠቅላላ ጉባኤው ይሁንታን አግኝቷል::
በዕለቱም ከአዲስ አበባ ኅብረት ሥራ ማኅበራት ማደራጃ የተወኩሉ አካላት ተገኝተዋል። በውይይቱም አባላት ለሸገር ኅብረት ሥራ ማኅበር ማደግ የሚበጁ ጠቃሚ ምክረ ሀሳቦችን በመስጠት ለህብረት ስራ ማህበራችን ግብዓት ሰጥተዋል። ጉባኤውም በውጤታማነት እንዲጠናቀቅ ትልቅ ሚና ነበራቸው።
ሸገር እስከዚህ ወር ድረስ 171 ሚሊዮን ብር ብድር ለአባላቱ የሰጠና ከ4703 በላይ የአባላት ቁጥር መድረሱን ለማወቅ ተችሏል::
©2016 ዓ.ም. ሸገር የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተ/መሰ/የኅብረት ሥራ ማህበር